« PreviousNext »

ናፍቆት

8 April 2008

በእኔና አንቺ መሀል ወንዝ አለ መራራ፣
አላገናኝ አለኝ፣ ሆኖኝ ባላጋራ፤
ያዘኝ ደሀነቴ ድልድይ እንዳልሠራ፣
ዋኝቼ እንዳልመጣ ውሀ ልቤ ፈራ፡፡
አንቺ ወዲያ ማዶ፣ እኔ ወዲህ ማዶ፤
ልባችን በስሜት ርቀቱን ጥሶ፣ ገደሉንም ንዶ፤
ልዩነት ጅረትም ፈሶ፤ ወርዶ፤ ወርዶ፤
ቀን ሳይሞላ አይቀርም ለኛ ተዋኅዶ፡፡
እስቲመቸኝ ድረስ፣ እስቲመችሽ ድረስ እስከዚያ ልጨነቅ፤
እስቲመጣ ጊዜ ያንን ወንዝ የሚያደርቅ፣
የስሜቴን ምሥጢር እስተዚያ ልደብቅ፣
ያንን ፈገግታሽን እነዚያ ዓይኖችሽን በናፍቆት ልጠብቅ፡፡

መስፍን ወልደ ማርያም፤ እንጉርጉሮ፣ 1967
* * *

Posted in Uncategorized | Trackback | del.icio.us | Top Of Page

No comments yet

Leave a Reply


*
To prove that you're not a bot, enter this code
Anti-Spam Image